ዲፕሎማ የሸሪዓ ትምህርት

የሁለተኛ ዙር ዲፕሎማ የሸሪዓ ትምህርት ፕሮግራም ምዝገባ ተዘግቷል።

መግለጫ

የተጠናከረ እውቀታዊ የሸሪዓ ፕሮግራም ሲሆን ጊዜ ገደቡ አንድ አመት ብቻ ነው። ስርዓተ-ትምህርቱ በአመት አንዴ ምዝገባው የሚከፍት ሲሆን እሱም ትምህርቱ ከመጀመሩ በፊት በቂ ጊዜ በማህበራዊ ሚዲያ እና በአፍሪካ ቲቪ ላይ ይፋ ይደረጋል። የዲፕሎማው ፕሮግራም በውስጡ ሁለት ሴሚስተር የያዘ ሲሆን ተማሪዎቹ በነዚህ ሁለት ሴሚስተሮች በየአንዳንዱ ሴሚስተር ውስጥ ስድስት የትምህርት አይነቶችን ይማራል። ተማሪው የሁለቱም ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና ካለፈ በኋላ ከአካዳሚው የማጠናቀቂያ ምስክር ወረቀት ይወስዳል።

በዲፕሎሙ ውስጥ የሚሰጡት ኮርሶች ትውውቅ

የትምህርት ማስተማሪያ መንገዶች

የሚነበቡ መፅሃፍት

በቪዲዮ መልክ የተቀዱ ሌክቸሮች

በኦዲዮ መልክ የተቀዱ ሌክቸሮች

በቲቪ ላይ የቀጥታ ስርጭት

የመማር ማስተማር እቅድ

አካዳሚው ከርቀት የማስተማር ስልትን የሚከተል ሲሆን ተማሪው ደግሞ በበኩሉ ከአሉት አማራጮች የሚመቸውን ይመርጣል። ትምህርቶቹም በቪዲዮ፣ በኦዲዮ እና በሃንዳውት መልክ ይቀርባሉ።

በመድረክ ላይ ያለውን የትምህርት ዕቅድ ዝርዝር በሙሉ ለማወቅ የተማሪ መመሪያ ደንብ ያውርዱ

የአስተማሪዎች ኮሚቴ አባል

ሼይኽ ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን

ሼይኽ ኑረላህ ሐሚዲን አብዱሰመድ

ሼኽ ሼይኽ ያዕቁብ መሐመድ ሀሰን

ሼኽ ሼይኽ ባህሩ ኡመር ሽኩር

ሼይኽ አብዱለጢፍ ጦሃ ሙሐመድ

ሼይኽ ሙሐመድ ፈረጀ መይግኑ